16.3 C
Asmara
Saturday, September 16, 2023

የምዕራባውያን የአዞ እምባ

ሲጀመር- አሁን በዓለምችን ላይ ላሉት ታላላቅ ችግሮች ሁሉ የመነሻ ምንጭ ምዕራባውያን ናቸው ብንል የተጋነነ አይደለም።ሲቀጥል- ምዕራባውያን ያላቸውን የሓይል ሚዛን ለመጠበቅ፣ አሁን የሚታዩትን ችግሮች ባሉብት ማስቀጠል፣ ለወደፊትም ተጨማሪ ችግሮችን መፍጠርና ችግሮቹን ማስተዳደር፣ የሚለው ፖሊሲያቸው ለዘመናት የሰሩበትና አሁንም በዋነኛነት የሚያራምዱት ነው።
ምንም እንኳን የችግሩ ምንጮች ምዕራባውያኖቹ ይሁኑ እንጂ፣ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በህኀላ እራሳቸው በቀጥታ ሳይሆን በተዘዋዋራ በሃገር-በቀል አሽከሮቻቸው አማካኝነት ነው ይህን እኩይ ፖሊሲያቸውን ሲያስፈጽሙ የቆዩት።አንዳንዴም እራሳቸው በቀጥታ በመግባት የማይስማሟቸውን መንግስታትን ገልብጠው፣ መሪዎቻቸውን ገድለው ወይም አስወግደው ሲያበቁ፣ እንደተለመደው በዴሞክራሲና በሰብአዊ መብቶች አላክው ይሳለቁብናል።
የሚደንቅ እና የሚገርም ነው። ሰውን በባርነት እንደ እቃ የሸጡ እና የለወጡ፣ አህዛብን እንደ ዲኖሳውርየር ከዓለም ገጽ ያጠፉ፣ በዘርኝነት የጥቁሮችን አእምሮ ከዝንጀሮ ጋር ያወዳደሩ፣ የሌሎችን መሬቶች በቀኝ ግዛት ወረው በመያዝ አህዛብን ያጎሳቆሉና ሃብቶቻቸውን የዘረፉ፣ እጆቻቸው በደም የበሰበሱ ምዕራባውያን፣ ተገልብጠው ስለ ሰብአዊነትና ስለ ዴሞክራሲ ለእኛ ሲሰኩን ይውላሉ። ብዙዎችም እውነት መስሏቸው አፋቸውን ከፍተው ይሰሟቸዋል።
እናም እንደ ኤርትራ ያሉ ጠንካራ፤ የሞራል ልእልና ያላቸው፣ የምዕራባውያንን ስነልቦና ጠንቅቀው የሚያቁ፣ ሃብታቸውን የማያስነኩ፣ አሽከርነትን የሚጠየፉ ሃገራት በምዕሪባውያን የሚወርድባቸው የተቀናጁ ጥቃቶችን መገመት አያዳግትም።
ብዙዎች ሃገራት ጥቃቱን መቋቋም ያቅታቸውና እጅ ይሰጣሉ። ኤርትራን ግን እጅ ማሰጠት አልተቻለም። ለወደፊቱም አይቻልም።ለምን ቢባል ኤርትራ በነበሩት እውነተኛ ታሪኮች እንጂ በትርክቶች የማታምን፣ ወጣቷን የምትገነባ፣ በራስዋ የምትተማመን፣ ሰርቶ በመለወጥ እንጂ በረድኤት የማታምን፣ ልመናን የምትጠየፍ፣ ሃብቷን መቆጣጠር የምትችልና የራስዋን ፖሊሲዎች የምትቀርጽ ሃገር ስለሆነች።
ብዙዎች ከላይ የተጠቀሱት በውንድሞቻችን ሃገር በኢትዮጵያ የሉም። ምክንያቱም ከዚ ቀደም በአተኩሮ ስላልተሰራባቸው።
አሁን በስልጣን ላይ ያለው የአብይ አህመድ መንግስት ኢትዮጵያን የምዕራባውያን ሳይሆን የኢትዮጵያውን ማድረግ እንደሚቻል በደንብ ገብቶታል። ይቻላልም!
ይኸው ኤርትራ ህያው ምስክር ነች።
ጥያቄው የአብይ መንግስት የምዕራባውያንን ሁለንተናዊ ጫና ተቋቁሞ ይሻገረዋል ወይ? የሚለው ነው።
ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ከመልካም ግረቤታቸው ከኤርትራና ከኤርትራውያን ብዙ መማር ይችላሉ።
አብይ ህዝቡን በማንቃት ረገድ ትልቅ ስራዎችን ከሰራ፣ ህዝቡሙ ትርጉም ከሌለው ትርክት እና የዘር ፖለቲካ ወጥቶ፣ ነቅቶ፣ ጥቅሙ ተረድቶትና የባለቤትነት ስሜትን ተላብሶ የአብይን መንግስት ከደገፈው፣ ኢትዮጵያም እንደ ኤርትራ የራሱዋ ባለቤት ትሆናለች።
ምዕራባዊያኖቹም ሌሎች ያልነቁባቸው ወይም ነቅተው ድፍረት ያጡት ጋር ሆደው የአዞ እምባቸውን ማፍሰሳቸውን ይቀጥላሉ።

Must read

ጅግንነት ኤርትራውያንን ኢትዮጵያውያንን ኣብ 50 ዓመቱ

ዓርቢ 08 ታሕሳስ 1972፡ ቅድሚ 50 ዓመት፡ ኣብ መዓርፎ ነፈርቲ ኣዲስ ኣበባ ሓደ ምንጋሩ ዘጸግም ፍጻሜ ተኻየደ። ኣብ ክሊ ዕድመ 24- 28 ዝርከቡ ሰለስተ ኤርትራውያንን ኣርባዕተ ኢትዮጵያውያንን ንነፋሪት ንመገዲ ኣየር ክጨውዩ ተበገሱ። እቶም ክልተ ተማሃሮ ዩኒቨርሲቲ፡ እቶም ኣርባዕተ ገሊኦም ትምህርቶም ዛዚሞም ኣብ ስራሕ ዝተዋፈሩ...

ናጽነት ከቢድ ዋጋ ከፊልካ ይመጽእ፣ ከቢድ ዋጋ እንዳኸፈልካ ድማ ይዕቀብ

"ዝሞተ ነይክሰስ ኣብ ሰማይ ነይሕረስ" እኳ እንተኾነ፣ ስቕ ዘየብል ክትዕዘብ እንከለኻ ስቕታ ኣይትመርጽን። "ኣዲኣ ገዲፋስ ሓትንኣ ትናፍቕ" ከምዝብሃል ብምኽንያት ሞት ንግስቲ ዓባይ ብርጣንያ ልዕልቲ ኤልሳቤጥ፣ መንግስቲ ኬንያ ናይ ሰለስተ መዓልታት ሃገራዊ ሓዘን ኣዊጁ ክትስምዕ ዘደንጹው እዩ። መቸም ብሰንኪ ምስፍሕፋሕን ጎበጣን ንግስነት ዓባይ ብርጣንያ ኣብ ሃገራትን...

ሓንጎል፡ ሓሞት፡ ደም

ኣብዚ ቀረባ ቕነ ንሓጺር እዋን ምስቲ ኣዝየ ዘድንቖ መራሒ ተራኺበ ከዕልል ዕድል ረኺበ ነይረ።  ምልክት ቃልሲ ኤርትራውያን ንናጽነትን ኣርካን ኣቦ ሰውራን ውሩይ መራሒ እዩ። ብትሑት ኣነባብራኡን ምቕሉልነቱን ዝፍለጥ ሰብ እዩ። ኣብ መዓልታዊ ህይወቱ ዝገብሮ ንጥፈታት ካብ ዝኾነ ተራ ዜጋ ዝተፈልየ ኣይኮነን። ከም ተራ ዜጋ ይኽደን፡ ኣብ መንጎ ህዝቡ ኣብ ንእሽቶ ገዛ ይነብር፡ ከምቲ ልምዲ ሕብረተሰብና ድማ ኣብ ኩሉ ማሕበራዊ ንጥፈታት ከም ዝኾነ ተራ ዜጋ ይሳተፍ። ኣብ መላእ ሃገር ብናጽነት ዝንቀሳቐስ፡ ምስ ህዝቡ ሕዉስ መራሒ...

Shida Friendship Forum

On the occasion of Eritrea’s 31st Independence Celebrations, Shida Media will live stream a panel discussion on Saturday 21st of May at 9AM LA time, 12PM NY time, 6PM Berlin time and 7PM Asmara and Addis Ababa time. The distinguished panelists are: Alemseged Tesfai -...

More articles

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

- Advertisement -spot_img

እዋናዊ ዜና