23.3 C
Asmara
Wednesday, September 13, 2023

የኢዜማ የፖለቲካ ዝሙት

ኢዜማ ትግራይን አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።
መግለጫው መግለጫ ሳይሆን፣ ኢዜማ በመጪው ምርጫ የትግራ ህዝብን ቀልብ በመሳብ የምርጫ ድምጽ ለማግኘት የተሰራ ርካሽ የፖለቲካ ዝሙት ነው።
ማን ጠርቶሽ አቤት አልሽ ይላሉ አበው።
የሚገርመው ደግሞ ኢዜማ በዚህ ርካሽ የፖለቲካ ዝሙታችው ኤርትራን በወያኔ ዘመን እንደተለመደው፣ ኤርትራን የሰይጣናዊ ስራዎች ምንጭ የሆነች ሃገር አርገው ለመቅረጽ መሞክራቸው ነው።
የኢዜማ ርካሽ ጨዋታ በዚህ ዘመን አይሰራም!
የኢትዮጵያ ህዝብ የኤርትራን ህዝብ እውነተኛ ምስል እና ማንነት በሚገባ ተረድቶታል።
በመጀመሪያ የኤርትራን ህዝብ፣ ሰራዊትና መንግስት ምን ያህል ጨዋ እንደሆኑ የኢዜማ መሪዎችና ተከታዬቻቸው በደንብ ጠንቅቀው ያውቃሉ።
ምክንያቱም የኢዜማ ዋና ጸሐፊ ፖሮፌሰር ብርሃኑ ጨለመ እና ተከታዮቻቸው ምድር እንደ ገሐነብ ብሆነችባቸው በዛ ክፉ ዘመን፣ ኤርትራ መስዋእት ከፍላ፣ ጨዋነትን አስተምራ፣ ገነት ሆና ብርሃኑንና ተከታዮቹን ለዚህ ያበቃችው ስለሆነች።
በመቀጠልም የወያኔ ጁንታ የሰሜን እዝ አባላትን በተኙበት ረሽና፣ ገሚሱን ወደ ኤርትራ አባራ፣ የተረፋትንም አስራ፣ 80% የሚጠጋውን የኢትዮጵያ ጦር መሳርያውን በቁጥጥር ስር አውላ ኢትዮጵያን የማፍረስ ስራዋን ስትጀምር፣ የኤርትራው መንግስትና ሰራዊት ሁኔታውን አንብቦ፣ ሩጫዋን ቀጭቶ፣ ያባረረቻቸውን የኢትዮጵያን ሰራዊት አባላት አደራጅቶና አስታጥቆ ሃሳቧን በአጭር እንዲቀር የአንበሳውን ድርሻ አስተዋጽኦ ባያደርግ ኖሮ፣ ብርሃኑ ጨለመና የኢዜማ ጀሌዎቹ አሁን ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር አትኖራቸውም ነበር።
ዳሩ ግን በትምህርት ካተማሩት ይልቅ በትርክት የሰሙትን ተረት እውነት አርገው በሚያዩ ሰዎች በሚመራ ኢዜማ፣ የፖለቲካ ዝሙት እንጂ ሌላ አይጠበቅም። በዚህ መግለጫም ይህንኑ ነው ያሳዩን።
ስለዚህ ነው ደግሞ የአመራር ብቃት ያሳየውን፣ ወያኔን ድባቅ የመታውን፣ የኤትራን መልካም ጉርብትና የሚፈልገውንና ኤርትራ በቀጠናው ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪነት የተረዳውን፣ የአብይ አህመድ የብልጽግናን መንግስት የመፎካከር አቅም የሌላቸው።
ኢዜማ መዝሙርና አሉባልታ እንጂ ስራና ክውንነት ምኑም ሆነው አያውቁም።

Must read

ጅግንነት ኤርትራውያንን ኢትዮጵያውያንን ኣብ 50 ዓመቱ

ዓርቢ 08 ታሕሳስ 1972፡ ቅድሚ 50 ዓመት፡ ኣብ መዓርፎ ነፈርቲ ኣዲስ ኣበባ ሓደ ምንጋሩ ዘጸግም ፍጻሜ ተኻየደ። ኣብ ክሊ ዕድመ 24- 28 ዝርከቡ ሰለስተ ኤርትራውያንን ኣርባዕተ ኢትዮጵያውያንን ንነፋሪት ንመገዲ ኣየር ክጨውዩ ተበገሱ። እቶም ክልተ ተማሃሮ ዩኒቨርሲቲ፡ እቶም ኣርባዕተ ገሊኦም ትምህርቶም ዛዚሞም ኣብ ስራሕ ዝተዋፈሩ...

ናጽነት ከቢድ ዋጋ ከፊልካ ይመጽእ፣ ከቢድ ዋጋ እንዳኸፈልካ ድማ ይዕቀብ

"ዝሞተ ነይክሰስ ኣብ ሰማይ ነይሕረስ" እኳ እንተኾነ፣ ስቕ ዘየብል ክትዕዘብ እንከለኻ ስቕታ ኣይትመርጽን። "ኣዲኣ ገዲፋስ ሓትንኣ ትናፍቕ" ከምዝብሃል ብምኽንያት ሞት ንግስቲ ዓባይ ብርጣንያ ልዕልቲ ኤልሳቤጥ፣ መንግስቲ ኬንያ ናይ ሰለስተ መዓልታት ሃገራዊ ሓዘን ኣዊጁ ክትስምዕ ዘደንጹው እዩ። መቸም ብሰንኪ ምስፍሕፋሕን ጎበጣን ንግስነት ዓባይ ብርጣንያ ኣብ ሃገራትን...

ሓንጎል፡ ሓሞት፡ ደም

ኣብዚ ቀረባ ቕነ ንሓጺር እዋን ምስቲ ኣዝየ ዘድንቖ መራሒ ተራኺበ ከዕልል ዕድል ረኺበ ነይረ።  ምልክት ቃልሲ ኤርትራውያን ንናጽነትን ኣርካን ኣቦ ሰውራን ውሩይ መራሒ እዩ። ብትሑት ኣነባብራኡን ምቕሉልነቱን ዝፍለጥ ሰብ እዩ። ኣብ መዓልታዊ ህይወቱ ዝገብሮ ንጥፈታት ካብ ዝኾነ ተራ ዜጋ ዝተፈልየ ኣይኮነን። ከም ተራ ዜጋ ይኽደን፡ ኣብ መንጎ ህዝቡ ኣብ ንእሽቶ ገዛ ይነብር፡ ከምቲ ልምዲ ሕብረተሰብና ድማ ኣብ ኩሉ ማሕበራዊ ንጥፈታት ከም ዝኾነ ተራ ዜጋ ይሳተፍ። ኣብ መላእ ሃገር ብናጽነት ዝንቀሳቐስ፡ ምስ ህዝቡ ሕዉስ መራሒ...

Shida Friendship Forum

On the occasion of Eritrea’s 31st Independence Celebrations, Shida Media will live stream a panel discussion on Saturday 21st of May at 9AM LA time, 12PM NY time, 6PM Berlin time and 7PM Asmara and Addis Ababa time. The distinguished panelists are: Alemseged Tesfai -...

More articles

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

- Advertisement -spot_img

እዋናዊ ዜና